የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከአምስቱ የኦርየንታል (ምስራቃዊ) ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክሪስቲያናት አንዷ ስትሆን። ኢትዮጵያ የክርስትናን እምነት ከተቀበለችበት ከ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ እስከ ጥር 6 ቀን 1943 ዓ.ም (1951 እ.ኤ.አ.) ድረስ የእስክንድርያ ኮፕት ቤተ ክርስቲያን ክፍል ነበር። በ1943 ዓ.ም ግን የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ባስልዮስ ከእስክንድርያው ፓትርያርክ አቡነ ዮሳብ 2ኛ የጵጵስና ማዕረግ ተቀበሉ። ኢትዮጵያም፤ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እራሷን የቻለች ሆነች። ወደ 40-45 ሚሊዮን የሚቀርቡ ምእመናን ሲኖሩት ከምሥራቃዊ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ትልቁ ነው
«ተዋሕዶ» ከልሣነ ግእዝ የመነጨ ቃል ሲሆን፡ ትርጒሙም «አንድ ሆኖ» ማለት ነው። ለዚሁም በዐረብኛ ተመሳሳይ ቃል «ታውሒድ» ሲባል በአንድ አምላክ ብቻ ማመን የሚለውን ፅንሰ ሀሳብ ያመለክታል።
No comments:
Post a Comment